TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ በአጭር የሞባይል መልዕክት የአባላት ምዝገባ ሊጀምር ነው

February 18, 2019
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ 6546 አጭር የፅሁፍ መልዕክትን በመጠቀም የአባላት ምዝገባ እና የእርዳታ ማሰባሰብ ስራዎችን ሊጀምር ነው፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ይህን ይፋ ያደረገው የካቲት 05 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡
 
የቅርንጫፉ ኃላፊ አቶ አበባው በቀለ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ላለፉት 38 ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረው የቤት ለቤት የአባላት ምዝገባ ዘዴ ኋላ ቀር በመሆኑ ይህን አጭር የፅሁፍ መልዕክት መጀመር በርካታ ሰዎች አባል እንዲሆኑና የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
 
ዶ/ር ሚርጌሳ ካባ የቅርንጫፉ ቦርድ ሊቀመንበር በበኩላቸው፣ አዲስ አበባ የተለያዩ ሀገራዊና አለምአቀፋዊ ተቋማት መቀመጫ መሆኗን ገልፀው አጭር የፅሁፍ መልዕክቱን መጠቀም የቅርንጫፉን አባላት ቁጥር ለመጨመር እና ሀብት ለማሰባሰብ የተሻለ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ኢትዮ ቴሌኮም ላደረገው ድጋፍ የቦርድ ሊቀመንበሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
 
ማንኛውም ሰው በ6546 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ያለምንም ክፍያ ከተመዘገበ በኋላ በ6547 አባል ሆኖ መመዝገብ እንዲሁም በ6548 ደግሞ የፈለገውን መዋጮ በማድረግ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሚያከናውናቸውን ሰብዓዊ ተግባራት ማገዝ እንደሚቻል ታውቋል፡፡
 
አጭር የፅሁፍ መልዕክቱ አገልግሎት ከሳምንት በኋላ በይፋ እንደሚጀምር በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ተገልጿል፡፡
 
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ካሉት አጠቃላይ 6.1 ሚሊዮን አባላት ውስጥ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ወደ ሁለት መቶ ሺህ አባላት እንዳሉት አቶ አበባው ገልፀዋል፡፡

Calendar

February 2019
M T W T F S S
 123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728  
« Jan   Mar »

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83/ +251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X