TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

ማኅበሩ ለግጭት ተጎጂዎች የቅርብ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አስታወቀ

September 1, 2021

ከማኅበሩ ቅርንጫፎች በተገኘ መረጃ በሰሜን ጎንደር ደባርቅ 15 ሺህ፣ በደቡብ ወሎ ደሴ ላይ 110 ሺህ እንዲሁም በዋግምራ ከ20 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በእነዚህ ቦታዎች በአጠቃላይ 23 አምቡላንሶችን በማሰማራት 1500 ለሚሆኑ ተጎጂወች የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እርዳታ እና ፅኑ ህሙማንን ወደ ጤና ተቋማት የማድረስ ሰብዓዊ ተግባር ተከናውኗል፡፡

በሰሜን ጎንደር የተለያዩ አካባቢዎች 13 እንዲሁም በደቡብ ወሎ 4 ድንኳኖችን በመትከል ለተፈናቃይ ወገኖቻችን ጊዜያዊ መጠለያ እንዲያገኙ ጥረት ተደርጓል፡፡ ለተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ይዘት ያላቸውን ብስኩቶች፣ የማብሰያ እና ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና የተለያዩ አልባሳት ድጋፍ ተሰጥቷል፡፡

ግጭቶች ባሉባቸው ቦታዎች የጤና ተቋማት ላይ እየደረሰ በሚገኘው የሥራ ጫና ምክንያት የመድኃኒት እና ሌሎችም ለተቋማቱ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች እጥረት ድጋፍ ይሻሉ፡፡ ማኅበሩ በዚህ በኩል ለጎንደር ከተማ፣ ለጭልጋ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ደሴ፣ ሀይቅ፣ ኮምቦልቻ፣ ዳንግላ ፣መራዊ እና አዴት ለሚገኙ የጤና ተቋማት የማደንዘዣ መድኃኒት/ Anesthesia/ ጨምሮ ልዩ ልዩ መሰረታዊ መድኃኒቶች፣ዊልቼር፣ የህክምና አልባሳት እና የመኝታ ቁሳቁሶች አበርክቷል፡፡ በአጠቃላው በደቡብ ጎንደርና በደቡብ ወሎ ለ 20 ሺኅ ተረጂዎች ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር ማህበሩ ዕርዳታ አድርጓል፡፡

በቅርቡ በአማራ ክልል ሰሜን እና ደቡብ ወሎ ዞን፣ ሰሜን ጎንደር እና ዋግምህራ አካባቢዎች የአምቡላንስ እና የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና እርዳታ፣ የምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች እና የተለያዩ መሰረታዊ የሆኑ መድኃኒቶች ድጋፍ አድርጓል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ማህበሩ ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለ12 ሺህ ተፈናቃዮች ደሴ ላይ እርዳታ በማደል ላይ ይገኛል፡፡ ተመሳሳይ እርዳታም ለደቡብ ጎንደር ተፈናቃዮች በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚደረግ ታውቋል፡፡

ህብረተሰቡም እንደተለመደው በቆይታ ግዜ ሊበላሹ የማይችሉ ምግቦች፣ አልባሳት፣ የመመገቢያ እና ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና ሌሎችም ድጋፎችን ስታዲዮም አካባቢ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት እና አቅራቢያችሁ ወደሚገኙ የማኅበሩ ቅርንጫፎች በመሄድ ትብብር እንድታደርጉ እንጠይቃለን፡፡

የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የምትፈልጉ ከዚህ በታች የተጠቀሰው የማኅበሩን የኢተዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር በመጠቀም ድጋፍ ማድረግ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡

                                                                                              ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1 000000 902 008

Calendar

September 2021
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930  
« Aug   Dec »

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83/ +251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X