TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሜቴ  ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር   የአምቡላንስ ድጋፍ አደረገ።

ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሜቴ  ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር   የአምቡላንስ ድጋፍ አደረገ።
July 10, 2025News

ድጋፉ በአገሪቱ የተለያየዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ሳቢያ  ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ አምቡላንሶችን ለመተካት ያለመ መሆኑም ተጠቁሟል።

ሐምሌ 03፣2017 አዲስ አበባ

የኢትዮጵየ ቀይ መስቀል ማኅበር ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በድጋፍ የተበረከቱለትን  14 አምቡላነሶች ዛሬ ተረክቧል፡፡የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዋና ፀሓፊ አቶ አበራ ሉሌሳ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በኢትጵያ ቀይ መስቀል ማኅበርና በአለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ መካከል ያለው አጋርነት አመታትን የተሻገረና  በመጠንም በስፋትም እያደገ የመጣ መሆኑን አንስተዉ ኮሚቴው የማህበሩን የሎጀስቲክስ አቅም በመገንባት ረገድ ከፍተኛ  ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡

በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በሚከሰቱ ግጭቶች ሳቢያ የኢትጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ንብረት የሆኑ አምቡላንሶች፤ቢሮዎች፤መገልገያ ቁሳቁሶችና ሌሎች ንብረቶች  መውደማቸዉን ያስታወሱት አቶ አበራ በዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ድጋፍ ግን  ዳግም ወደ ስራ መግባት ተችሏል ብለዋል፡፡ለዚህም ለኮሚቴው ያላቸውን ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአለም ዓቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተወካይ አቶ ዘውዱ አያሌው  በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት፡ ድጋፉ ማኅበሩ እየሠጠ ያለውን ህይወት የማዳን ተግባር በተሻለ ጥራትና ቅልጥፍና ለመስጠት ያስችለዋል ያሉ ሲሆን ትብብሩ በአጋርነት መንፈስ ይቀጥላልም ብለዋል።አለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ያላቸው ትብብር ብዙ መልክና ገፅታ ያለው ነው ያሉት ተወካዩ ፤ይህ የአምቡላስ ድጋፍም በሁለቱ ሰብዓዊ ተቋማት መካክል ለዘመናት የዘለቀው የትብብርና የአጋርነት መንፈስ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

የማህበሩ ስራ አመራር ቦርድ አባል ዶ/ር አዲስ አለም ሙላት በዚሁጊዜ  ቦርዱን በመወከል ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ላለፉት 90 ዓመታት በሰብዓዊ ተግባራት ላይ በመሰማራት ህብረተሰቡን ሲያገለግል መኖሩን አስታውሰው፤በድጋፍ የተገኙት አምቡላንሶች የማህበሩን ህይወት የማዳን ተልዕኮ በማገዝ ረገድ ሚናቸው የጎላ ነው ብልዋል፡፡

በኢትዮጵየ ቀይ መስቀል ማኅበር የአደጋ ስጋት ስር አመራር መምሪያ ተወካይ የሆኑትአቶ ጋሻው ዳኜ በርክክቡ ወቅት ባስተላፉት መልዕክት ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል  ኮሚቴ ማህበሩን ለመደገፍ እያደረገ ያለውን ያላሰለሰ አስተዋፅዎ አድንቀዋል፡፡

በአሁኑ ወቅትም ከ7መቶ በላይ አምቡላንሶችን በመላው አገሪቱ በማሠማራት የህይወት አድን ተግባሩን እያከናወነ የሚገኘው የኢትዮጵየ ቀይ መስቀል ማህበር  ፤ በድጋፍ ያገኛቸውን አምቡላንሶች በአማራ፤ኦሮሚያ፣ጋምቤላ፣ደቡብ ኢትዮጵያ፣ሀረሪና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች  ለሚገኙ የማህበሩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች  አስተላልፏል።

ከቀናት በፊት 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በድምቀት ያከበረው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል የአምቡላስ አገልግሎት የጀመረው እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1944 ዓ.ም ነበር።ማህበሩ ላለፉት ዓመታት በሚሰጠው የ24 ሰዓት ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ህይወት የመታደግ ተልዕኮውን በትጋት እየተወጣም ይገኛል፡፡

Calendar

July 2025
M T W T F S S
 123456
78910111213
14151617181920
21222324252627
28293031  
« Dec   Aug »

Categories

  • News
  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83/ +251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X