TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

ማኅበሩ የአምቡላንስና የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ

ማኅበሩ የአምቡላንስና የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ
October 29, 2025News

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ተራድኦ የጋራ ብልፅግና አገራት ድርጅትጋር በመተባበር በደቡብ ወሎ ዞን ለሚገኙ የጤና ተቋማት ከ76 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸውን አምቡላንሶችና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

የተደረገውንም ድጋፍ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የደቡብ ወሎ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን እና ድጋፍ ለተደረገላቸው ወረዳዎች የሥራ ኃላፊዎች አስረክቧል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በ90 ዓመታት በርካታ ሰብዓዊ፣ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማቶች ያከናወነ መሆኑን የደቡብ ወሎ ዞን ቅንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ ቸኮል ገልጸው፤ማህበሩ ባለፉት ዓመታት አገልግሎትን በማስፋፋትና በማጠናክር እየሠራ እንደሚገኝም አመልክተዋል። እያንዳንዳቸው 18 ሚሊዮን ብር ወጭ የተደረገባቸው ሁለት አምቡላንሶች ለተንታ ወረዳ እና ለለጋምቦ ወረዳ ድጋፍ መደረጉን አክለዋል።

በተጨማሪም ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ተራድኦ የጋራ ብልፅግና አገራት ድርጅት ጋር በመተባበር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው በለጋምቦና ጃማ ወረዳ ለሚገኙ የጤና ተቋማት ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የመድሀኒት፣የህክምና ቁሳቁስና ማሽነሪ ድጋፍ ስለመደረጉም ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር በስሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው የጤና ተቋማት ከዚህ ቀደምም አምቡላንሰ ፣ በፀሐይ ጉልበት የሚሰሩ የመጠጥ ውኃና መሰረተ ልማትና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ያውሱት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌታቸው በለጠ ናቸው::

አምቡላንስ ድጋፍ መደረጉ በወሊድ ምክንያት የእናቶችን ሞት ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ ያግዛል። አምቡላንሶቹ ለድንተኛ አደጋ ህክምና ለመስጠት የሚያስችል ቁሳቁስ የተሟላቸው ዘመናዊና ምቹ መሆናቸውንም ነው አቶ ጌታቸው የጠቀሱት።

የመድሀኒት እና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፎቹም በጤና ተቋማት የነበውን እጥረት መቅረፍ ስለሚችሉ የማኅበረስቡን እንግልት ከመቀነሱም በላይ በቀጠይ ለጤና ተቋማቱ የፋይናንስ ግብኣት ምንጭ እንደሚሆኑ አቶ ጌታቸው አመልክተዋል። ድጋፎቹ በአግባቡ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም ጠቁመዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን እንዳሉት ደግሞ የአምቡላንሶቹ ድጋፍ እናቶችና ህጻናትን ጨምሮ አደጋ የደረሰባቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ፈጥኖ ወደ ጤና ተቋማት ለማድረስ በዞኑ የነበረውን እጥረት ያቃልላል።

የመድሀኒት ድጋፍም ከዋጋ ጋር ተያይዞ በጤና ተቋማት የነበረውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም ነው አቶ አሊ የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሕዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በብዙ ነገሮች እየደገፈ በመሆኑ በእጅጉ ሊመስገን ይገባል ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው አቶ አሊ መኮንን።

በድጋፋ ከመድሀኒት በተጨማሪ አልትራ ሳውንድ፣ ኬሚስትሪ ማሽን፣ ማይክሮስኮፕ፣ የደም መመርመሪያ እና መሰል ከማዋላጃ ጋር የተያያዙ ቁሳቁሶች ይገኙበታል።

ዘገባው የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነው

Add Comment Cancel

You must be logged in to post a comment.

Calendar

October 2025
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
2728293031  
« Sep    

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83/ +251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X