TOLL FREE NUMBER: 907

Our Branches

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
    • Our Branches
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • E-Learning
    • Train with Us
    • Tenders
    • Vacancy
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
  • Contact

ወጣቶች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረከቡ

February 17, 2021

የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላም ማህበር በትግራይ ክልል በግጭት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል፡፡ የካቲት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በማህበሩ በኩል ለተጎጂዎች በቀጥታ እንዲደረርስ የተሰጠው ድጋፍ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመትና የምግብ፣ የአልባሳት፣ የህጻናት አልሚ ምግቦችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመወከል ድጋፉን ያስረከቡት አቶ አቢዮት በላቸው ‹‹ይህንን ድጋፍ ያደረግነው ለትግራይ ህዝብ ያለንን ወገናዊነት ለመግለጽ ነው›› ብለዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህን መሰል ድጋፍ ለማድረግ የተሳተፉትን ጓደኞቻቸውንና የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላምና ለልማት ማህበር አባላትና በጎ ፈቃደኞችን አመስግነዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላምና ለልማት ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ቦና ደበላ በበኩላቸው ‹‹የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ጥሪ ተቀብለን አባላቶቻችንንና በጎ ፈቃደኞቻችንን በማስተባበር ይህንን ድጋፍ ማድረግ በመቻላችን ደስታ ተሰምቶኛል፡፡›› ብለዋል፡፡ አያይዘውም በቀጣይም በሁሉም የሃገራችን አካባቢዎች በተለያዩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለመደገፍ አቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ በማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በኩል ድጋፉን የተረከቡት የማኅበሩ ምክትል ዋና ፀሐፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው በራስ ተነሳሽነት የሚደረጉ መሰል ድጋፎች አጋርነትን ከማሳየት ባለፈ እንደ ሃገር ችግሮችን በራስ አቅም ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡ አቶ እንግዳ አክለውም ሌሎች የማህበረሠቡ ክፍሎች በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመደገፍ እጆቻቸውን እንዲዘረጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከለጋሾች የተበረከተው ድጋፍ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አማካኝነት ለሚመለከታቸው ተጎጂዎች በቀጥታ እንደሚደርስ ማኅበሩ ገልጿል፡፡

በቀጣይ መርዳት ለምትፈልጉ፡- በኢ.ቀ.መ.ማ የባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000327016559 (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) በኩል ማገዝ ይችላሉ፡፡

Calendar

February 2021
M T W T F S S
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
« Jan   Mar »

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

#EthiopiaZeroHunger #FundamantalPriciples #Humanity #IFRC AfricaZeroHunger DanishRedCross Dissemination EC2R Emblem EmergencyResponse ERCS Ethiopian Red Cross Ethiopian RedCross EthiopianRedCross FCDO FinnishRedCross Front Page FundamantalPriciples FundamentalPrinciples HumanitarianCommunication Humanity Humanityfirst ICRC IFRC IHL Mastercardfoundation Migration MoH NetherlandsRedCross NewStructute PNS RCRC RedCrossDissemination RFL SaferAccess SaferAccessframework SaferAccessFrameworl SLL StaffManagementMeeting Tigray TogetherForChange UK UNICEF UniteForZeroHunger ZeroHungerCampaign

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarters

+251-115-18-01-81

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Register for Trainings
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Tenders
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X