TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Risk Management
    • Peace Building
    • Volunteers & Membership
    • Image Building
    • Capacity Building
    • Resource Mobilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

19ኛው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ

July 29, 2022
“ያለፉት ሦስት አመታት ሕዝባችንና አገራችን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የነበርንበትና እና ከዚህም ውስጥ ለመውጣት በጋራ ትግል ያደረግንበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ጉዞ ውስጥ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ የዜጎችን ህይወት ታድጓል፣ የተከፉትን፣ ልባቸው የተሰበረ ቤተሰቦችን አንገት ቀና ለማድረግ ችሏል፡፡” ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የማኅበሩ የበላይ ጠባቂ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ካደረጉት ንግግር (ሐምሌ 9/2014) በጠቅላላው ጉባዔ ላይ በተደረገው የአመራር ቦርድ አባላት ምርጫ አምስት በድጋሚ፣ አራት አዲስ ተመርጠዋል፡፡ በድጋሚ የተመረጡት የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ቶላ ቀደም ሲል ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር፡- “የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ሁልጊዜ ቅድሚያ ለሰብኣዊነት የሚለውን መርህ አጥብቆ ያራምዳል፡፡ በዚህ መርህ ዙሪያ ያጠነጠነ ክንውንም ያደርጋል፡፡ ለምናደርገው መልካም ነገር፣ ለሚሰማን ፍቅርና መልካም ስሜት እንዲሁም በደስታና ፍሰሃ የሚሞላውም የኛ አእምሮና አካል ነው፡፡ ለዚህም የተሳካ ጉዞ የማህበሩ ሰራተኞች፣ በጎፈቃደኞች፣ አባላት፣ መንግስት፣አጋሮቻችን፣ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ አካላት ዋናዎቹ የስኬታችን ባለቤቶች ናቸው፡፡ “ ብለዋል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው ላይ 250 ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን 173 ቱ ከክልል የቀይ መስቀል ቅርንጫፎች የመጡ ናቸው፡፡ ማኅበሩን ለሚቀጥሉት አራት አመታት እንዲመሩ የተመረጡት የኢቀመማ የአመራር ቦርድ አባላት የሚከተሉት ናቸው፡
1. አቶ አበራ ቶላ፣ ፕሬዚዳንት
2. ዶ/ር ፎዚያ አሚን፣ ምክትል ፕሬዚዳንት
3. ወ/ሮ ሒክመት አብደላ፣ አቃቤ ነዋይ
4. ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፣ አባል
5. ፕሮፌሰር አብርሃም ኃ/አምላክ፣ አባል
6. አምባሳደር ዶ/ር ቶፊቅ አብዱላሂ፣ አባል
7. ዶ/ር አዲስአለም ሙላት፣ አባል(የወጣቶች ተወካይ)
8. ኢንጂነር ጌታሁን ሁሴን፣ አባል
9. ዶ/ር ሰይፉ ጌታሁን፣ አባል
May be an image of 4 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 4 people, people sitting and people standing

 

Calendar

July 2022
M T W T F S S
 123
45678910
11121314151617
18192021222324
25262728293031
« Jun   Aug »

Categories

  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X