TOLL FREE NUMBER: 907

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • CCDHS
    • Vacancy
    • Procurement
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
    • E-Learning
    • Mobile App
  • Contact

ኮካ ኮላ ኩባንያ ለማኀበሩ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

April 7, 2020

በሀገራችን ከፍተኛ አደጋ አየጋረጠ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ አ.ማ /ኮካ ኮላ ኩባንያ/ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡

መጋቢት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ድጋፉን አስመልክቶ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የኮሮና ቫይረስ ዜናን በፈረንጆቹ ታህሳስ 2019 ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ በህዝባችን ላይ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ዝግጅት እያደረገ መቆየቱን የገለፁት የማኀበሩ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ፣ በተለይም ታዋቂ የሀገሪቷ አርቲስቶችን፣ የኢትዮ ጃዝ ሙዚቃ ፈጣሪ ዶ/ር ሙላቱ አስታጥቄ፣ ደራሲ አያልነህ ሙላቱ፣ አርቲሰት አለማየሁ እሸቴ፣ ፋንቱ ማንዶየ፣ ንዋይ ደበበንና አረጋኸኝ ወራሽን እንዲሁም በሲኒማ ኢንደስትሪው ታዋቂ የሆነውን አርቲስት መኮንን ለአከን በመያዝ በከተማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ላይ ከፍተኛ የማኀበራዊ ንቅናቄ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

ዋና ፀሐፊው ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ኩባንያ ማኀበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማኀበሩ ይህንን የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው ድጋፉን አስመልክተው በመላው የቀይ መስቀል አባላቶችና በጐ ፈቃደኞች ስም አመስግነዋል፡፡ ወደፊትም ኩባንያው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋቸውን  ገልፀዋል፡፡

ማህበሩ የተገኘውን የገንዘብ እርዳታ በተለይም ከፍተኛ ቁጥር ላላቸው በመዲናዋ ጐዳናዎች ላይ ወድቀው ለሚገኙ ወጣቶች፣ ሴቶችና አዛውንቶች የምግብ ድጋፍ እንደሚውልም ተመልክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የኮካ ኮላ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዳረል ዊልሰን በበኩላቸው ኮሮና ቫይረስ በዓለማችን ታሪክ ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሰብዓዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን አመልክተው ኩባንያቸው ችግሩን ከግምት በመውሰድ ድጋፍ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን አቅም በፈቀደ ሁኔታ ከጎናቸው እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ጋር አያይዘው ኩባንያቸው የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘሮችንም ማምረትና ማከፍፈል እንደሚጀምር ገልፀው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቫይረሱን በትብብር ለመግታት እንዲቻል ሀኪሞች የሚሰጡትን መመሪያ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ልክ እንደ አሁን ቀደሙ ሁሉ ወደፊትም ከኢትዮያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመልክቷል፡፡

Calendar

April 2020
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930  
« Mar   May »

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarter

+251-115-18-01-83/ +251-115-18-01-83

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Procurement
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X