TOLL FREE NUMBER: 907

Our Branches

  • Donate
HealthFlex
×
  • Home
  • Who We Are
    • About us
    • Patron
    • Governance
    • Where We Work
    • Our Branches
  • What We Do
    • Disaster Preparedness and Response
    • Disaster Risk Reduction and Community Resilience
    • Health and Wellbeing
    • Members, Volunteer and Youth Engagement and Management
    • Humanitarian Diplomacy and Communication
    • Partnership Development and Management
    • Institutional and Leadership Transformation
    • Resource Development, Mobilization and Utilization
  • Get Involved
    • Donate
    • Be a Volunteer
    • Be a Member
    • E-Learning
    • Train with Us
    • Tenders
    • Vacancy
  • Media Hub
    • News
    • Publication
    • Feature Stories
    • Events
    • Gallery
      • Photos
      • Videos
  • Get help
    • Restoring Family Links
    • Ambulance Services
  • Contact

የማኅበሩ ሠራተኞች በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከአዲሱ ዋና ፀሀፊ ጋር ተወያዩ

March 3, 2021

                                                                       ጥር 17፣ 2013 ዓ.ም ዋና ፀኃፊ ሆነው በድጋሚ ወደ ማኅበሩን የተቀላቀሉት አቶ ጌታቸው ታዓ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል የዋናው ፅህፈት ቤት ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም በማኅበሩ ማሠልጠኛ ማዕከል ከዋና ፀኃፊ አቶ ጌታቸው ታዓ ጋር ባካሄዱት የትውውቅ እና የምክክር መድረክ ማኅበሩን በሚመለከት ትኩረት ይፈልጋሉ ያሉዋቸው ጉዳዮችን አንስተው በጋራ መክረዋል፡፡

በመድረኩ ላይ ትውውቅ ያደረጉት አቶ ጌታቸው ታዓ፤ ከ1993-1997 ማኅበሩን በኃላፊነት መምራታቸውን እና በቀጣይም በዓለም ዓቀፉ የቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፈዴሬሽን ውስጥ በልዩ ልዩ ኃላፊነቶች ላይ የተለያዩ አገራት በመዘዋወር ሠብዓዊነትን ሲያገለግሉ እንደቆዩ አስታውሰዋል፡፡ በመጨረሻም በዘርፉ ያካበቱትን ጠቃሚ እውቀት እና ልምድ ይዘው ሠብዓዊነትን አንድ ብሎ ወዳስጀመራቸው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል በመመለሳቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡ ዋና ፀኃፊው አክለውም ያላቸውን ሙሉ አቅም እና ግዜ ተጠቅመው የማኅበሩን አገልግሎት እና ተደራሽነት ለማሻሻል እንደሚተጉ አስረድተው፤ ለሚጠበቀው የጋራ ውጤት ሁሉም የማኅበሩ ባልደረቦች በኃላፊነት ስሜት ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

በመድረኩ ከሠራተኞች እና ከሌሎች ሥራ ኃላፊዎች የማኅበሩን ሥራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ የተለያዩ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በጎ ፈቃደኞች እና አባላት ፣ የአምቡላንስ አገልግሎት እና የማኅበሩ ሀብት አሰባሰብ ትኩረት ካገኙ ሀሳቦች መካከል ናቸው፡፡ ማኅበሩ በበጎፈቃደኞች እና አባላት ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ የምልመላ እና አስተዳደር ሥራው ቀዳሚ ትኩረት እንደሚሰጠው በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል፡፡

ማኅበሩ ከሚያከናውናቸው ሠብዓዊ ተግባራት መካከል የአምቡላንስ አገልግሎት ዋነኛው ነው፡፡ ከቅርብ ግዜ ወዲህ በሀገሪቱ የተፈጠሩ ግጭቶችን ተከትሎ የወደሙ እና የት እንዳሉ የማይታወቅ ጥቂት የማይባሉ አምቡላንሶች እንዳሉ፤ ሁኔታው ማኅበሩ የሚከተላቸውን መርሆዎች መሠረት አድርጎ የሚሠጠውን አገልግሎት እንዲስተጓጎል አድርጓል፡፡ ችግሩን በመሠረታዊነት ለመቅረፍ ትምህርተ ቀይ መስቀል ከታች ለሚገኘው የመንግስት መዋቅር እና ለሚመለከታቸው የህብረተሰቡ ክፍሎች አጠናክሮ መስጠት እንደሚገባ ዋና ፀሀፊው አመላክተዋል፡፡

በመጨረሻም ማኅበሩ የቆመለትን ዋና ዓላማ ‹ሰብዓዊነት› ማዕከል በማድረግ በተፈጥሮም ሆነ ሠው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት ለሚደርስባቸው ወገኖች ያለምንም ልዩነት ህዝብን ለማገልገል ቃል በመግባት ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

Calendar

March 2021
M T W T F S S
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
293031  
« Feb   Apr »

Categories

  • Feature Stories
  • News

Tag Cloud

#EthiopiaZeroHunger #Humanity #swedishinternationaldevelopmentcooperation AfricaZeroHunger AICS AmericanRedCross Benishangu;Gumuz CountCarlGustav DisasterResponse EC2R Embassyof theNetherlands EPHI ERCS EthiopianRedCross Ethiopian Red Cross FCDO FinnishRedCross Front Page Gamo GamoLandSlide GermanRedCross Humanity Humanityfirst ICRC IFRC IHL ItalianRedCross Judith Weeks landslide Middleeast MoH NetherlandsRedCross NLRC PNS RCRC ResourseMoblisation SaferAccess schoolofhumanity SiltieZone swedishembassy SwedishRedCross Tigray UK UniteForZeroHunger WeLiveForHumanity

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society Headquarters

+251-115-18-01-81

ercsinfo@redcrosseth.org

P.O.Box: 195

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Donate
  • Register for Trainings
  • Be a Volunteer
  • Be a Member
  • Vacancy
  • Tenders
  • Partners link
  • FAQ

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
  • TikTok
  • LinkedIn
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System
X